am_tn/job/10/12.md

1.7 KiB

ህይወት እና የቃል ኪዳን ታማኝነት ሰጠኸኝ

"ህይወት" እና "ታማኝነት" የሚሉት ረቂቅ ስሞች "ህያው" እና "ታማኝ" በሚል ሊገለጹ ይችላሉ፡፡ "አንተ ለቃል ኪዳንህ ታማኝ ነበርክ ደግሞም ህያው እንድሆን ፈቅደሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስያሜ የሚለውን ይመልከቱ)

የአንተ እርዳታ

"የአንተ እንክብካቤ"

መንፈሴን ጠበቀ

እዚህ ስፍራ ኢዮብ የተወከለው "በመንፈሱ" ነው፡፡ "ጠበቅከኝ" ወይም "እኔን በጥንቃቄ ተመለከትክ" ወይም "በደህንነት/በሰላም ጠበቅከኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

እነዚህ አንተ በልብህ የሰወርካቸው ነገሮች

እዚህ ስፍራ "እነዚህ ነገሮች" የሚለው የሚያመለክተው ከተከታዩ ቁጥር ላይ የሚገኘውን ነገር ነው

እነዚህ አንተ በልብህ የሰወርካቸው ነገሮች

እዚህ ስፍራ "አንተ በልብህ የሰወርካቸው" ማለት እግዚአብሔር ምስጢር አድርጓቸዋል ወይም ደብቆታል ማለት ነው፡፡ "አንተ ምስጢር ያደረካቸው እነዚህ ነገሮች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

አንተ ታውቀዋለህ

"አንተ ትጠብቀኛለህ"