am_tn/job/10/10.md

2.0 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በእነዚህ ሀረጋት፣ ኢዮብ እግዚአብሔር እንዴት በእናቱ ማህጸን ውስጥ እንዳበጀመው ለመግለጽ የሸክላ ሰራተኛን ቋንቋ ይጠቀማል፡፡ (ስነ ግጥም የሚለውን ይመልከቱ)

እንደ ወተት አላፈሰስከኝምን፣ እንደ እርጎስ አላረጋኸኝምን?

ይህ አዎንታዊ ምላሽ የሚጠብቅ ጥያቄ ነው፡፡ "እንደ ወተት አፈሰስከኝ እንደ እርጎ አረጋኸኝ" ወይም "ፈሳሽ ወተት እርጎ እንደሚሆን በማህጽን አበጀኸኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

አንተ

እዚህ ስፍራ "አንተ" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው

እኔ

እዚህ ስፍራ "እኔ" የሚለው የሚያመለክተው ኢዮብን ነው፡፡

ቆዳ እና ስጋ አለበስከኝ

እግዚአብሔር የኢዮብን አካል በቆዳ እና ስጋ መሸፈኑ የተገለጸው እግዚአብሔር ኢዮብን እንዳለበሰው ተደርጎ ነው፡፡ "ሰውነቴን በቆዳ እና ስጋ ሸፈንክ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

በአንድነት አገጣጠምከኝ

"በአንድነት ሸመንከኝ፡፡" እግዚአብሔር የኢዮብን አካል በማህጸን ማዋደዱ የተገለጸው እግዚአብሔር ጨርቅን እንደሸመነ ተደርጎ ነው፡፡ "አዋደድከኝ/በአንድነት አደረግከኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ጅማቶች

ጡንቻን ከአጥንት ወይም ከሌላ የሰውነት ክፍል ጋር የሚያያይዝ እና ነጭ ጠንካራ ማስተሳሰሪያ