am_tn/job/10/08.md

1.1 KiB

የአንተ እጆች

እዚህ ስፍራ "እጆች" የሚለው የሚወክለው የእግዚአብሔርን እና የእርሱን የመፍጠር ድርጊት ነው፡፡ "አንተ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

የአንተ እጆች አበጁን ሰሩኝም

ኢዮብ እግዚአብሔር እንዴት በጥንቃቄ እርሱን እንደፈጠረው ለመግለጽ ሸክላ ሰሪ ሸክላውን የሚያበጅበትን አሰራር በዘይቤ ይጠቀማል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

አበጀኝ ሰራኝም

"ቅርጽ ሰጠኝ ሰራኝ" "ቅርጽ ሰጠኝ" እና "አበጀኝ" የሚሉት ቃላት በትርጉም ተመሳሳይ ናቸው፡፡ (ጥንድ ትርጉም የሚለውን ይመልከቱ)

ልብ በል

"አስታውስ"

ዳግም ወደ አፈር አምጣኝ

"እንደገና ወደ አፈር መልሰኝ"