am_tn/job/09/34.md

1.4 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

እነዚህ ቁጥሮች በኢዮብ እና በእግዚአብሔር መካከል ገብቶ ሊዳኝ የሚችል ከእግዚአብሔር የሚበልጥ ማንም እንደሌለ ቀደም ሲል የቀረበውን ክርክር ይቀጥላሉ

የአግዚአብሔርን በትር ከእኔ ውሰድ

እዚህ ስፍራ "የእግዚአብሔር በትር" የሚለው እግዚአብሔር ኢዮብን መቅጣቱን ወይም ማረሙን የሚገልጽ ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "እግዚአብሔር እኔን መቅጣቱ ይቁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ማስፈራራቱ ከእኔ ይቁም

"ፍርሃት" የሚለው ረቂቅ ስም "አስፈራራ" በሚል ግስ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እርሱ እኔን ማስፈራራቱን እና ማስፈራቱን ማን ባስቆመልኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ከዚያ እኔም እናገራለሁ

"ቀጥሎ እናገራለሁ"

ነገሮች አሁን ባሉበት

"ምክንያቱም አሁን ነገሮች እንዲህ ናቸውና"