am_tn/job/09/32.md

2.0 KiB

እመልስለታለሁ

ኢዮብ እግዚአብሔር ስህተት ሰርተሃል ብሎ እንደከሰሰው ያመለክታል፣ እርሱም ለክሶቹ መልስ መስጠት እንደሚፈልግ ይናገራል፡፡ "ላቀረበብኝ ክስ ምላሽ እንድሰጥ" ወይም "እራሴን እንድከላከል" ወይም "ከእርሱ ጋር ስለ ንጹህነቴ እንድከራከር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

አብረን ወደ ፍርድ/ችሎት እንግባ

"ወደ ፍርድ/ችሎት አብረን እንግባ፡፡" እዚህ ስፍራ "ፍርድ ቤት" የሚለው ሰዎች ቀርበው ዳኛ ለክርክራቸው መፍት የሚሰጥበትን ቦታ ነው፡፡ "አብሮ ወደ ፍርድ ቤት መግባት" እርስ በእርስ ተካሶ ወደ ፍርድ ቤት መሄድን የሚያመለክት ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ "እውነቱ እንዲወጣ በዳኛ ፊት አንዱ ከሌላው ጋር መከራከር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በመካከላችን ዳኛ የለም

ይህ ማለት በኢዮብ እና በእርሱ መሃል ከእግዚአብሔር የሚበልጥ ምን ትክክል እንደሆነ ሊወስን የሚችል ዳኛ የለም ማለት ነው፡፡

በሁለታችንም ላይ እጁን የሚጭን

እዚህ ስፍራ "እጁን የሚጭን" ማለት የበለጠ ስልጣን ወይም ሃይል ያለው ማለት ነው፡፡ "እጁን በሁለታችንም ላይ የሚያኖር" ወይም "በሁለታችንም ላይ ስልጣን ያለው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)