am_tn/job/09/27.md

2.9 KiB

ስለ ማማርርባቸው ነገሮች እረሳለሁ

"ምሬት" የሚለው ረቂቅ ስም "ማማረር" በሚለው ግስ መተርጎም ይችላል፡፡ "ማማረሬን አቆማለሁ" ወይም "በእግዚአብሔር ላይ ማማረሬን አቆማለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

ማማረሬን

ኢዮብ በማን ላይ እንደሚያማርር በግልጽ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "በእግዚአብሔር ላይ ማማረሬን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

ሃዘንተኛ ፊቴን መልሼ ደስተኛ እሆናለሁ

የኢዮብ ሀዘንተኛ ገጽ የተገለጸው አንድ ዞር ሊደረግ እንደሚችል ነገር ተደርጎ ነው፡፡ ሀዘንተኛ ሆኜ መታጠቴን አቁሜ ፈገግ እላለሁ፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ሀዘኖቼ ሁሉ ያስፈሩኛል

ኢዮብ በቁጥር 27 የተናገረውን ቢያደርግ ሊከተል የሚችለውን ውጤት ቁጥር 28 እና 29 ይገልጻሉ፡፡ ይህ "ከዚያ" የሚለውን ቃል በመጨመር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ከዚያም ከሀዘኖቼ ሁሉ የተነሳ እፈራለሁ" (አያያዝ ቃለት/መስተጻምር የሚለውን ይመልከቱ)

ከሀዘኔ ሁሉ የተነሳ

"ሀዘን" የሚለው ረቂቅ ስም በግስ መልኩ ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ከጎዱኝ ነገሮች ሁሉ የተነሳ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

እኮነናለሁ

"ተጠያቂ እሆናለሁ ደግሞም እቀጣለሁ፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "እግዚአብሔር ይፈርድብኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይምተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

ታዲያ ስለምን በከንቱ እደክማለሁ?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚጠቀመው የእግዚአብሔርን ፊት ለማግኘት የሚያደደርገው ሙከራ ምንም ጥቅም እንደማያስገኝለት ማሰቡን በትኩረት ለመግለጽ ነው፡፡ ኢዮብ ሊያደርግ እየሞከረ ስለሚገኘው ነገር በውስጠ ታዋቂነት የሚገኘው መረጃ ግልጽ ሊደረግ ይቻላል፡፡ "የእግዚአብሔርን ፊት ለማግኘት መሞከሬ አንዳች ጥቅም የለውም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)