am_tn/job/09/19.md

2.8 KiB

ይህ የጥንካሬ ጉዳይ ቢሆንም

"የጥንካሬ መፎካከሪያ ቢኖርም"

እነሆ፣ እርሱ ታላቅ ነው

"ተመልከት እርሱ ታላቅ መሆኑን ትረዳለህ" ወይም "እኔ ልነግርህ ለተዘጋጀሁት ነገር ትኩረት ስጥ፡ እርሱ ታላቅ ነው"

እርሱ ታላቅ ነው

"እርሱ ከሁሉ ታላቅ ነው"

ለእርሱ ማን የክስ መጥሪያ ሊያቀርብለት ይችላል?

ይህ ጥያቄ "ከቶ ማንም" የሚል ምላሽ እግዚአብሔርን ወደ ፍርድ ቤት ሊያቀርበው አይችልም የሚል ምላሽ ያሰጣል፡፡ ይህ በገለጻ መልክ ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ማንም ለእርሱ መጥሪያ ሊያቀርብለት አይችልም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡(ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ምንም እንኳን ጻድቅ/ትክክለኛ ብሆንም፣ የገዛ አንደበቴ ይፈርድብኛል፤ እንከን የለሽ ብሆንም ቃሎቼ ይኮንኑኛል፡፡

ይህ ሀረግ ተመሳሳይ ሃብን ሁለት ጊዜ ደግሞ በማቅረብ አጽንኦት ይሰጣል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ትክክለኛ/ጻድቅ ብሆንም

እዚህ ስፍራ "እኔ ትክክለኛ ነኝ" የሚለው ትክክለኛ የሆነውን ያረግኩት እኔ ነኝ ማለት ነው፡፡ "ምንም እንኳን ትክክለኛ ነገሮችን ባደርግም" ወይም "ምንም እንኳን እኔ ንጹህ ብሆንም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ስማዊ ቅጽሎች የሚሉትን ይመልከቱ)

የገዛ አንደበቴ ይኮንነኛል/በደለኛ ያደርገኛል

እዚህ ስፍራ "አንደበት" የሚለው የኢዮብን ቃላት ነው፡፡ "የራሴ ቃላት ይከሱኛል" ወይም " የተናገርኩት ይኮንነኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

ነውር ባይኖርብኝም

"ጥፋት/እንከን ባይኖርብኝም"

የራሴ ቃሎች ጥፋተኛ መሆኔን ያሳያሉ

እዚህ ስፍራ "የራሴ ቃሎች" የሚለው የተገለጸው ቃላቶቹ ራሳቸው እርምጃ መውሰድ እንደሚችሉ ተደርጎ ነው፡፡ "እግዚአብሔር እኔ የተናገርኩትን የእኔኑ ጥፋተኝነት ለማረጋገጥ ይጠቀምበታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ጥፋተኛ

እዚህ ስፍራ ይህ ቃል "ገልበጥባጣ" ወይም "ጠማማ" የሚል ትርጉም አለው፡፡