am_tn/job/09/16.md

1.4 KiB

በአውሎ ነፋስ ሰብሮኛልና

ኢዮብ ከእግዚአብሔር ዘንድ የመጣበትን መከራ ከአውሎ ነፋስ ተጽዕኖ ጋር ያነጻጽረዋል፡፡ "በአውሎ ነፋስ እንደተጎዳሁ ጎድቶኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

አውሎ ነፋስ

ጥቃት የሚያደርስ ሀያለኛ ነፋስ

ቁስሌን አበዛው

"ብዙ ቁስሎች አደረገብኝ" ወይም "ደጋግሞ አቆሰለኝ"

ያለ ምክንያት

"ምንም እንኳን እንዲህ እንዲያደርግ የሚያበቃ ጥፋት ባልሰራም" ወይም "ምንም እንኳን ንጹህ ብሆንም"

ትንፋሽ እንዳገኝ

ይህ ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን ትርጉሙ "ደግሜ መተንፈስ እንድችል" (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ በመራራነት ሞላኝ

ይህ ቁጥር እግዚአብሔር የኢዮብን ህይወት እንዲመረር በሚያደርጉ ነገሮች እንደሞላው ይናገራል፡፡ "መራርነት" የሚለው ረቂቅ ስም "መራራ" በሚለው ቅጽል ሊገለጽ ይችላል፡፡ "በመራራ ነገሮች ሞላኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ረቂቅ ስሞች የሚሉትን ይመልከቱ)