am_tn/job/09/10.md

1.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው በእነዚህ በእያንዳቸው ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን በመገልገል ድርብ ሃሳቦችን ተጠቅሞ የእግዚአብሔርን ታላቅነት፣ የማይታይ መሆኑን እና ሉዓላዊነቱን በአንድ ሃሳብ ለማስተላለፍ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የማይደረስባቸው/የማይመረመሩ ነገሮች

"ለመረዳት የማይቻሉ ነገሮች"

እነሆ

"ተመልከት" ወይም "አድምጥ" ወይም "ልነግርህ የተዘጋጀሁትን ለመስማት ትኩረት ስጥ፡፡"

እርሱ አለፈ

"እርሱ በዚያ አለፈ" ወይም "እርሱ ተንቀሳቀሰ"

እርሱ አንዳች ነገር ቢነጥቅ፣ ማን ሊያስቆመው ይችላል? እርሱን ‘ምን እያደረግህ ነው' ብሎ ሊጠይቀው የሚችል ምን ነው?

እነዚህ "ማንም" የሚል ምላሽ ሚጠበቅባቸው ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎች ናቸው፡፡ በገለጻ መልክ ሊጻፉ ይችላሉ፡፡ "እርሱ አንድ ነገር ቢወስድ፣ ማንም ሊያስቆመው አይችልም፡፡ ማንም ‘ምን እያደረግህ ነው?' ሊለው አይችልም፡፡ በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ አንዳች ነገር ቢነጥቅ

"እርሱ አንድ ነገር ቢወስድ" ወይም "እርሱ አንድ ነገር መንጠቅ ቢፈልግ"