am_tn/job/08/06.md

1.7 KiB

አጠቃላይ መረጃዎች፡

በልዳዶስ ኢዮብ ንጹህ ቢሆን ኖሮ እግዚአብሔር ይረዳው ነበር ይላል‹ ነገር ግን በልዳዶስ ኢዮብ ንጹህ መሆኑን አያምንም፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

ንጹህ እና ትክክለኛ ብትሆን

"ንጹህ እና ጻድቅ ሰው ብትሆን ኖሮ" ወይም "እግዚአብሔርን ታዝዘህ ቢሆን እና ትክክለኛ የሆነውን ነገር የምታደርግ ቢሆን ኖሮ"

እርሱ ስለ አንተ ይነሳል

እዚህ ስፍራ ያህዌ የተገለጸው ኢዮብን ለመርዳት ከእንቅልፉ እንደተነሳ ተደርጎ ነው፡፡ "አንተን ሊረዳህ" ወይም "ለአንተ መልካም ነገሮችን ለማድረግ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

አንተን ወደ ትክክለኛ ስፍራ ይመልስሃል

ይህ የሚያመለክተው ኢዮብ ያጣቸውን ነገሮች፤ ቤተሰቡን ጨምሮ፣ ሀብቱን እና ክብሩን መልሶ እንደሚሰጠው ነው፡፡

ምንም እንኳን ጅማሬህ እጅግ ታናሽ ቢሆንም፣ ፍጻሜህ ግን እጅግ ታላቅ ይሆናል

እዚህ ስፍራ ሀብትን ማጣት የተገለጸው "ታናሽ ጅማሬ" እንደሆነ ተደርጎ ነው፡፡ "በህይወትህ መነሻ ላይ ደሃ ብትሆንም፣ በዕድሜህ የኋልኛ ዘመን እግዚአብሔር እጅግ ባለጠጋ ያደርግሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)