am_tn/job/08/04.md

1.6 KiB

ለእጃቸው ኃጢአት አሳልፎ ሰጥቷቸው ከሆነ

እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚወክለው የኃጢአትን ሀይል ወይም ውጤት ነው፡፡ በልዳዶስ እግዚአብሔር የኢዮብን ልጆች የገደላቸው በኃጢአታቸው ምክንያት እንደሆነ ያመለክታል፡፡ "የልጆችህ ኃጢአት እግዚአብሔር እንዲገድላቸው ምክንያት ሆኖታል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)

ነገር ግን አንተ ምናልባት እግዚአብሔርን በትጋት ፈልገህ ጥያቄህንም ሁሉን ቻይ ለሆነው አቅርበህ ይሆናል

በልዳዶስ ኢዮብ ከእግዚአብሔር ጋር በትክክል ቢስማማ ምን ሊሆን ይችል እንደ ነበረ እየተናገረ ነው፤ ነገር ግን በልዳዶስ ኢዮብ ይህንን ማድረጉን አያምንም፡፡ (መላምታዊ ሁኔታዎች የሚለውን ይመልከቱ)

በትጋት እግዚአብሔርን መፈለግ… ሁሉን ቻይ ለሆነው ጥያቄህን ማቅረብ

እነዚህ ሁለት ሀረጋት ኢዮብ እግዚአብሔርን እርዳታ ወይም ምህረት መጠየቁን ያመለክታሉ፡፡ (ጥንድ ትርጉም የሚለውን ይመልከቱ)

በትጋት እግዚአብሔርን መፈለግ

"ከልብ እግዚአብሔርን እርዳታ መጠየቅ"