am_tn/job/07/19.md

1.4 KiB

ምራቄን ለመዋጥ…ይህ ለምን ያህል ጊዜ ይሆና?

እዚህ ስፍራ ኢዮብ ሁለት የተለያዩ ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎችን በመጠቀም አንድን ሀሳብ የሚገልጸው እግዚአብሔር እርሱን መከታተሉን ቢያቆም ደስ እንደሚለው ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ "እኔን መከታተልህን አቁም! የራሴን ምራቅ የምውጥበትን ያህል ጊዜ እንኳን ፋታ ስጠኝ!" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚሉትን ይመልከቱ)

ምራቅ

አፍ እርጥበቱን እንዲጠብቅ እና ምግብን ለመዋጥ የሚረዳ በሰዎች አፍ ውስጥ የሚፈጠር ፈሳሽ

ኃጢአት ብሰራ እንኳን … ሸክም ሆንኩብህ?

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያቀርበው እግዚአብሔር የማይገባ ነገር እንዳደረሰበት ከእርሱ ጋር ለመከራከር ነው፡፡ " ኃጢአት ብሰራ እንኳን፣ አንተ ሰዎችን ሁሉ ስለምታይ ያ በአንተ ላይ አንዳች አያደርግም፡፡ ሸክም እሆንብህ ዘንድ፣ ለምን ኢላማህ እንዳደረግከኝ ንገረኝ፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)