am_tn/job/07/16.md

1.8 KiB

አያያዥ ሃሳብ፡

ጸሐፊው የኢዮብ መከራ በእርሱ ማንነት እርባና ግንዛቤ ላይ ትኩረት ለመሰጠት ሁለት የተለያዩ አገላለጾችን በመጠቀም እንድን ሃሳብ ለማስተላለፍ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን መጠቀሙን ይቀጥላል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ህይወቴን ጠላሁ

"ህይወቴን ናቅኩት"

ሁሌም በህይወት ለመኖር

"ለዘለአለም ለመኖር"

ቀናቴ/ዘመኔ እርባና ቢስ ናቸው

"ዘመኔ አለ ፍሬ ነው" ወይም "የህይወቴ ቀናት ከንቱ/ባዶ ናቸው"

ትከታተለው ዘንድ …. ሰው ምንድን ነው?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው እግዚአብሔር ለሰው ለምን ትኩረት እንደሚሰጥ መደነቁን ለማጉላት ነው፡፡ ይህ በዐረፍተ ነገር ሊተረጎም ይችላል፡፡ "ትከታተለው ዘንድ…ሰው ምንድን ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ልብህን ታሳርፍበት ዘንድ

እዚህ ስፍራ ልብ/አእምሮ የመሚለው የሚወክለው ሃሳብን እና ትኩረት መስጠትን ነው፡፡ "ልብህን ታሳርፍበት ዘንድ" ማለት ትኩረት መስጠት ማለት ነው፡፡ "ትኩረትህን ወደ እርሱ ታደርግ ዘንድ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

እርሱን ተመልከተው

"እርሱን በጥንቃቄ መርምረው"