am_tn/job/07/13.md

2.2 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው የኢዮብን ጥልቅ መከራ ለማጉላት ሁለት የተለያዩ አገላለጾችን በመጠቀም እንድን ሃሳብ ለማስተላለፍ በመጀመሪያዎቹ ሁለት ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን መጠቀሙን ይቀጥላል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

መኝታዬ ያጽናናኛል፣ መከዳዬ ማጉረምረሜን ቀለል ያደርግልኛል

እዚህ ስፍራ "መኝታ/አልጋ" እና "መከዳ" የሚሉት "እንቅልፍ" ለሚለው ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ነው፡፡ ኢዮብ ለመተኛት ጋደም ሲል አረፍ ለማለት ተስፋ ያደርጋል፡፡ ይህ ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት/ ሰብአዊ ባህሪያትም ደግሞ አሉት፤ የማጽናናት እና ሰውን አረፍ የማድረግ አቅም አላቸው፡፡ "መኝታዬ እና መከዳዬ እንደ ሰው ያሉ ነገሮች ናቸው፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

አልጋዬ/መኝታዬ… መከዳዬ

እነዚህ ሀረጋት ተመሳሳይ ነገርን ያመለክታሉ፡ "አልጋዬ…መኝታዬ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

አንተ አሰደነገጥከኝ/አስፈራኸኝ

እዚህ ስፍራ "አንተ" የሚለው የሚያመለክተው እግዚአብሔርን ነው

ማነቅ

አንድን ሰው ጉሮሮውን ጨምቆ እና ትንፋሹን አቁሞ መግደል

እነዚህ የእኔ አጥንቶች/አጥንቶቼ

እዚህ ስፍራ ኢዮብ "አጥንቶች" የሚለውን ቃል የተጠቀመው አካሉን ለማመልከት ነው፡፡ "ይህ የእኔ አካል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)