am_tn/job/07/11.md

2.3 KiB

በመንፈሴ ጭንቀት እናገራለሁ፣ በነፍሴን መራርነት አማርራለሁ

ኢዮብ ዝም የማይልበትን ምክንያት ለማጉላት ሁለት የተለያዩ ገለጻዎችን በመጠቀም አንድን ሃሳብ ያስተላልፋል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አፌን አላቅብም

እዚህ ስፍራ አፍ የሚወክለው ንግግርን ነው፡፡ "ንግግሬን አልገድብም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በመንፈሴ ምሬት

"በመንፈሴ ሀዘንተኝነት" ወይም "በመከራዬ ስቃይ፡፡" "ጭንቀት" የሚለውን ረቂቅ ስም "ስቃይ" የሚለውን ተውሳከ ግስ ተጠቅሞ መተርጎም ይቻላል፡፡ "መንፈሴ ተጨንቆ ሳለ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

በነፍሴን መራርነት

እዚህ ስፍራ ሀዘን የተገለጸው መራራ ጣዕም እንዳለው ተደርጎ ሲሆን፣ "ነፍስ" ደግሞ የሰውን ሁለንተና የሚያመለክት ሆና ተነግራለች፡፡ "በቁጣ እና ቅር በመሰኘት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር እና ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚሉትን ይመልከቱ)

በእኔ ላይ ጠባቂ ታኖር ዘንድ እኔ ባህር ነኝ፣ ወይንስ የባህር አውሬ ነኝ?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚያቀርበው በእግዚአብሔር ላይ ማዘኑን ለመግለጽ ነው፡፡ ኢዮብ ራሱን ከባህር ወይም ከባህር አውሬ ጋር በማነጻጸር እግዚአብሔር እርሱን አሰቃቂ ፍጥረት አድርጎ እንደቆጠረው ይናገራል፡፡ ይህ በገለጻ ሊተረጎም ይችላል፡፡ "እኔ ጠባቂ የሚያስፈልገው የባህር አውሬ ወይም ባህሩን አይደለሁም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ዘይቤያዊ አነጋገር የሚሉትን ይመልከቱ)