am_tn/job/07/08.md

2.7 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው ኢዮብ ከሞት በኋላ እግዚአብሔርም ሆነ እርሱን የሚያውቁት ሰዎች ዳግም እንደማያዩት ያለውን ሀሳብ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ እንዲሁም አንድን ሀሳብ ሁለት የተለያዩ ገለጻዎችን በመጠቀም ለማስተላለፍ በእነዚህ በእያንዳንዳቸው ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ መጠቀሙን ይቀጥላል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የሚመለከተኝ የእግዚአብሔር ዐይን ከእንግዲህ አያየኝም

በርካታ የመጽሐፍ ቅዱስ ትርጉሞች ይህንን "የሚመለከቱኝ ዐይኖች ከእንግዲህ አያዩኝም" በሚል ተርጉመውታል፡፡ "የእግዚአብሔር" ቃሎች በዚህ ሀረግ ላይ የተጨመሩት በይዘቱ ውስጥ የተካተቱ/የተጠቆሙ በመሆኑ ነው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

የሚመለከተኝ የእግዚአብሔር ዐይን… የእግዚአብሔር ዐይን በእኔ ላይ ይሆናል

እዚህ ስፍራ እግዚአብሔር ምን እንደሚመለከት ትኩረት ለመስጠት የተወከለው በእርሱ "ዐይን" ነው፡፡ "እኔን የሚመለከት እግዚአብሔር… እግዚአብሔር ይመለከተኛል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ደመና እንደሚበን እና እንደሚጠፋ፣ ወደ ሲኦል የሚወርድ ዳግም አይመለስም

ኢዮብ ሞትን የሚገልጸው በኖ እንደሚጠፋ ደመና ነው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚልን ይመልከቱ)

ደመና እንደሚበተን

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ "ደመና እንደሚበን" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

ወደ ሲኦል የሚወርድ ዳግም አይመለስም

"የሞተ ተመልሶ አይመጣም"

በእርሱ ስፍራ/በስፍራው

"በእርሱ ስፍራ" የሚሉት ቃላት በእርሱ ስፍራ የሚኖሩትን ይወክላል፡፡ "በእርሱ ስፍራ የሚኖሩ ሰዎች" ወይም "የእርሱ ቤተሰቦች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)