am_tn/job/06/21.md

2.5 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በእነዚህ ቁጥሮች ኢዮብ ወዳጆቹን ለመገሰጽ እና ከእነርሱ አንዳች እርዳታ አለመጠየቁን ለማጉላት አራት ጥያቄዎችን ያነሳል፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

አሁንም

ኢዮብ ይህንን ሀረግ የሚጠቀመው እየተናገረ የሚገኘውን ነገር ዋና ክፍል ለመጀመር ነው

እናንተ ወዳጆቼ ለእኔ አንዳች አላደረጋችሁም

"የእናንተ ወዳጅነት ለእኔን ምንም አልባኝም"

ፈርታችኋል

ይህ ማለት ኢዮብ ያለበትን ችግር አይተዋል፤ እናም በተመሳሳይ ሁኔታ ውስጥ እንዳይገቡ ፈርተዋል፡፡ "እግዚአብሔር ተመሳሳይ ነገር ያደርስብናል ብላችሁ ፈርታችኋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

እናንተን ‘አንዳች ነገር አድርጉልንኝ ብያችኋለሁ?' ወይስ፣ ‘ከሀብታችሁ ስጦታ ስጡኝ ብያችኋለሁ?' ወይስ፣ ‘ከጠላቴ እጅ አድኑኝ ብያችኋለሁ?' ወይስ ‘ከጨቆነኝ እጅ ተቤዡኝ ብያችኋለሁ?'

ኢዮብ ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የተጠቀመው እርሱን ወዳዶቹ አንድም ነገር እንዲሰጡት ወይም እንዲያደርጉለት አለመጠየቁን ለማጉላት ነው፡፡ "ገንዘብ ወይም ስጦታ እንድትሰጡን ጠየቅኳችሁን፡፡ ወይንስ ከጠላቶቼ ወይም ከጨቋኞቼ እንድታድኑኝ ጠይቄያችኋለሁ፡፡በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ከጠላቶቼ እጅ እንድኑኝ…ከጨቋኞቼ እጅ ተቤዡኝ

እነዚህ ሁለቱም አገላለጾች ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ እንደዚሁም፣ እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚወክለው ሃይልን ወይም መቆጣጠርን ነው፡፡ "ከጠላቶቼ ወይም ከጨቋኞቼ አድኑኝ" ወይም "ከባላኝጣዎቼ አድኑኝ" በሚው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ዘይቤያዊ አና ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚሉትን ይመልከቱ)

ተቤዡኝ

"አድኑኝ"