am_tn/job/06/14.md

3.9 KiB

እያበቃለት/እየደከመ ላለ ሰው፣ ወዳጆቹ ታማኝነትን ሊያሳዩት ይገባል

ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "አበቃልኝ/ደከምኩ ላለ ሰው ወዳጁ ታማኝ ሊሆንለት ይገባል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)

እየደከመ ያለ ማን ነው

ይህ የሚናገረው፣ በአካል እየደከመ የመጣ ስለሚመስል፣ ተስፋ ስለ ቆረጠ እና በችግሩ ስለተዋጥ ሰው ነው፡፡ "ተስፋ የቆረጠ ማን ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ሁሉን ቻይ የሆነውን ፍርሃት ለሚፈልግ እንኳን

"ሁሉን ቻይ የሆነውን አምላክ መፍራት ቢያቆም እንኳን፡፡" ለዚህ ሊሰጡ የሚችሉ ትርጉሞች 1) የደከመ/ያበቃለት ሰው እግዚአብሔርን አይፈራም ወይም 2) የእርሱ ወዳጆች እግዚአብሔርን አይፈሩም

ወንድሞቼ ለእኔ የነበራቸው ታማኝነት እንደ በረሃ ጅረት ነበር

ኢዮብ ወዳጆቹ ለእርሱ ታማኝ አለመሆናቸውን የሚገልጸው በድንገት እንደሚደርቅ "በክረመት እንደሚሞላ ደረቅ ወንዝ" ነው፡፡ እንደዚሁም ኢዮብ እዚህ ስፍራ ወዳጆቹን በምጽት "ወንድሞች" እያለ ይገልጻቸዋል፡፡ "ወዳጆቼ ለእኔ ታማኝ አይደሉም፡፡ እነርሱ እንደ በረሃ ጅረት ናቸው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻታሪ ዘይቤ እና ምጸት የሚሉትን ይመልከቱ)

ወዴትም እንደማይደርስ የውሃ ቦይ

"እንደሚደርቅ ጅረት ውሃ፡፡" ኢዮብ ስለ ወዳጆቹ እንደ ሚደርቅ ወራጅ ሊታመኑባቸው የማይቻል መሆኑን መናገሩን ይቀጥላል፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ደግሞም ራሱን በውስጣቸው ከሚደበቀው በረዶ የተነሳ…በላያቸው ካለው በረዶ የተነሳ የሚጠቁሩ/የሚደፈርሱ

እነዚህ ሁለት ሀረጋት ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ ወራጁ ውሃ/ትንሽ ወምዝ በክረምት እንዴት በበረዶ እንደተሞላ ይገልጻሉ፡፡ "በክረምት በበረዶ በመሸፈናቸው ጠቁረው/ደፍርሰው ይታያሉ፤ ደግሞም በቀለጠው በረዶ/አመዳይ ይሞላሉ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)

ከበረዶው የተነሳ ራሱን በእነርሱ ውስጥ የሚደብቅ

ይህ የሚናገረው በረዶው እየቀለጠ ራሱን በወራጁ እንደሚደብቅ ውሃው ወደ ወንዙ እንደሚሄድ ነው፡፡ "ምክንያቱም በረዶው እየቀለጠ ወደ እነርሱ ይሄዳል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

አየሩ ሲሞቅ/በጋ ሲመጣ፣ ይጠፋሉ… ሞቃት ሲሆን ከስፍራቸው ይቀልጣሉ

እነዚህ ሁለት ሀረጋት ተመሳሰይ ትርጉም አላቸው፡፡ በበጋ/በሞቃቱ ወቅት ወራጁ ወንዝ እንዴት እንደሚደርቅ ይገልጻሉ፡፡ "በጋ ሲመጣ፣ በረዶ ይቀልጣል ወራጁም ወንዝ ይደርቃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚሉትን ይመልከቱ)