am_tn/job/06/12.md

1.9 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው በእነዚህ በእያንዳንዳቸው ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ጥያቄዎችን የተጠቀመው ኢዮብ መከራውን ለመቋቋም አቅም ማጣቱን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ብርታቴ የድንጋይ ጥንካሬ ነውን? ወይንስ ስጋዬ የተሰራው ከነሀስ ነው?

ኢዮብ የሰውነቱን ደካማነት ለማጉላት እንደ አለት እና ነሀስ ጠንካራ አይደለሁም በማለት ይገልጻል፡፡ እነዚህ ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎች በገለጻ መልክ ሊቀርቡ ይችላሉ፡፡ "እንደ አለት ጠንካራ አይደለሁም፡፡ ስጋዬ እንደ ብረት ጠንካራ አይደለም፡፡" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

እኔ…. በውስጤ እርዳታ የሚሆነኝ አለመኖሩ እውነት አይደለምን?

ኢዮብ ይህንን ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚጠቀመው እውቀት እንዳጣ እና ደካምነቱን አጉልቶ ለማሳየት ነው፡፡ እንደዚሁም ደግሞ፣ "በውስጤ እርዳታ የሚሆነኝ የለም" የሚለው ፈሊጣዊ አነጋገር ነው፡፡ " እኔ…የቀረ አቅም የሌለኝ መሆኑ እውነት ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ጥበብ ከውስጤ ተሟጦ ወጥቷል

"ስኬቴ ከእኔ ተወስዷል፡፡" ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ጥበቤ ከእኔ ርቋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚለውን ይመልከቱ)