am_tn/job/06/10.md

1.8 KiB

ይህ እንኳን መጽናናት በሆነኝ ነበር

"ይህ መጽናናት ያምጣልኝ፡፡" "ይህ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው እግዚአብሔር እርሱ/ኢዮብ እንዲሞት መፍቀድን ነው፡፡ "ሞቴ መጽናናት በሆነኝ" ወይም "መሞቴ ያጽናናኝ" (ይሆናል ተብሎ የሚገመት ዕውቀት እና በውስጠ ታዋቂነት የሚገኝ መረጃ የሚለውን ይመልከቱ)

በመከራዬ ብፈነድቅ እንኳን ይህም ጭምር ስቃዬን አይቀንሰውም

"ማብቂያ በሌለው ስቃይ ደስታን ላገኝ እቸኩላለሁ" ወይም "የማይጠፋ መከራ በጽናት እታገሳለሁ"

መፈንደቅ

"መደሰት"

አይቀንስም

"አይጠፋም"

የቅዱሱን ትዕዛዝ አልተላለፍኩም

"እግዚአብሔርን አልካድኩምና፡፡" ይህ በአዎንታዊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "ሁልጊዜም ቅዱሱን ታዝዣለሁ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

እታገስ ዘንድ ብርታቴ ምንድን ነው? ህይወቴ ይረዝም ዘንድ መጨረሻዬ ምንድን ነው?/ህይወቴ ስለ ምን ይቀጥላል?

ኢዮብ እነዚህን ጥያቄዎች የሚያነሳው መኖርን እንዲቀጥል የሚያደርግ ምንም ምክንያት እንደሌለው ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ እነዚህ ጥያቄዎች ሁሉም ተመሳሳይ ትርጉም አላቸው፡፡ በገለጻ መልክ ሊጻፉ ይችላሉ፡፡ "በህይወት ለመቀጠል በቂ ጥንካሬ የለኝም፤ ህይወቴ የሚቀጥልበት ምንም ምክንያት የለም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)