am_tn/job/06/07.md

1.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ኢዮብ ስለ መከራው መናገሩን እና መሞት መፈለጉን በገለጸ መጠን በእነዚህ ቁጥሮች ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን መጠቀሙን ይቀጥላል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እነርሱን መንካት አልፈልግም

"እነርሱ" የሚለው የሚያመለክተው መጥፎ ጣዕም ያላቸውን ምግቦች ነው፡፡

እኔን ለአንዴ እና ለመጨረሻ ጊዜ ለማድቀቅ

ይህ ማለት እግዚአብሔር እርሱ/ኢዮብ እንዲሞት ቢፈቅድ ማለቱ ነው፡፡ "ቢያደቀኝ እና እንድሞት ቢተወኝ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዩፊሚዝም/ የማያስደስትን ቃል ሻል ባለ ቃል መተካት የሚለውን ይመልከቱ)

ምነው ፈጥኖ እጆቹን ቢያነሳ እና ከዚህ ህይወት ቢቆርጠኝ

"ፈጥኖ እጆቹን ቢያነሳ" የሚለው ሀረግ ፈሊጣዊ አነጋገር ሲሆን በፍጥነት ማድረግን ይገልጻል፡፡ እንደዚሁም፣ "ከዚህ ህይወት ቢቆርጠኝ" የሚለው ሀረግ መግደል ለሚለው ዩፊሚዝም/ የማያስደስትን ቃል ሻል ባለ ቃል መተካት/ ነው፡፡ "ምነው ፈጥኖ ህይወቴን በአጭር ቢቆርጠው" ወይም "ፈጥኖ መጨረሳዬን ቢያደርገው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር እና ዩፊሚዝም/ የማያስደስትን ቃል ሻል ባለ ቃል መተካት እና የሚሉትን ይመልከቱ)