am_tn/job/06/01.md

1.2 KiB

ምነው ጭንቀቴ ቢመዘን፣ ስጋቴ በሚዛን ላይ ቢቀመጥ

እዚህ ስፍራ ጸሐፊው አንድ ሃሳብን፣ ይኸውም የኢዮብን መከራ ሸክም ለመግለጽ ሁለት የተለያዩ አገላለጾችን ይጠቀማል፡፡ ይህ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "መከራዬን መመዘን ብችል፣ ደግሞም ስጋቴን ሁሉ በሚዛን ላይ ባስቀምጥ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

በሚዛን ላይ

"በመለኪያ ላይ"

ከባህር አሸዋ የከበደ ይሆናል

ኢዮብ የመከራውን ክብደት ከአሸዋ ክብደት ጋር ያነጻጽራል፤ ሁለቱም አንድን ሰው ማድቀቅ የሚችሉ ናቸው፡፡ "ጭንቀቴ እና ስጋቴ በባህር ዳር ካለ አሸዋ ይከብዳል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ተነጻጻሪ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ንግግሬ የማያስገርሙ ነበሩ

"በግዴለሽነት ተናገርኩ" ወይም "በችኮላ ተናገርኩ"