am_tn/job/05/20.md

2.0 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በኢዮብ 5፡19 የሚጀምረው "እርሱ" ከሚለው "አንተ" ወደሚለው የተዋላጠ ስም/የስም ምትክ ሽግግር ማድረግ እሰከ ኢዮብ 5፡29 ማለትም የኤልፋዝ ንግግር እስከሚያልቅበት ድረስ ይቀጥላል፡፡ በረሃብ ጊዜ ይቤዥሃል እዚህ ስፍራ ማዳን የተገለጸው መቤዤት፣ መልሶ መግዛት እንደሆነ ተደርጎ ነው፡፡ "በርሃብ ጊዜ እግዚአብሔር ከአደጋ ያድንሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

የሰይፍ እጆች

እዚህ ስፍራ "እጆች" ምናልባት የሚወክለው ሰይፎችን ጨምሮ በመሳሪያ ጥቃት የሚያደርሱ ሰዎችን ሊሆን ይችላል፡፡ "ጥቃት የሚያደርሱ ሰዎች" ወይም "አንተን የሚያጠቁ ሰዎች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ስኔክቲክ/ የአንድን ነገር ስያሜ ከፊሉን በመውሰድ መላውን ነገር መግለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ከጥፋት

እዚህ ስፍራ "ጥፋት" የሚለው የሚያመለክተው በጠላት መደምሰስን ነው፡፡ "ያገኘህ ማንኛውም ጠላት ያጠፋሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ረቂቅ ስሞች የሚለውን ይመልከቱ)

በጥፋት እና ረሃብ ላይ ትስቃለህ

እዚህ ስፍራ "ሳቅ" የሚለው የሚገልጸው አለመፍራትን ነው፡፡ "ማናቸውንም የጥፋት አደጋ ወይም ረሃብ አትፈራም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ምልክታዊ/ትዕምርታዊ ቋንቋ የሚለውን ይመልከቱ)

የምድር አራዊት

ይህ የሚያመለክተው የዱር አራዊት ነው፡፡"የዱር እንስሳት" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)