am_tn/job/05/14.md

2.3 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው በእያንዳንዱ ቁጥር ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን አንድን ሀሳብ ሁለት የተለያዩ መግለጫዎችን በመጠቀም የሚያስተላልፈው እግዚአብሔር ክፉ ሰዎችን እንሚያዋርድ እና ድሆችን እንደሚያድን ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

በቀን ብርሃን ጨለማ ይገጥማቸዋል

እዚህ ስፍራ ለእግዚአብሔር የማይመቹ ክፉዎች እና ጨካኝ ሰዎች ፀሐይ በአናት ትክክል ሳለች፣ በቀን ብርሃን እነርሱ ግን በጨለማ ውስጥ እንደሚገኙ ይናገራል፡፡ ማድረግ የሚፈልጉትን አንዳች ነገር ማድረግ አይችሉም፣ ምክንያቱም ማየት አይችሉም፡፡ "ተንኮለኞች፣ በእኩለ ቀን እንኳን በጨለማ ውስጥ ናቸው" (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ዳበሳ

እንደ ዐይነ ስውር ዙሪያን መዳሰስ

እኩለ ቀን

የቀኑ እኩሌታ፣ ፀሐይ በአናት ትክክል የምትሆንበትና ከፍተኛ ብርሃኗን የምትሰጥበት ጊዜ

እርሱ ግን ደሃውን ከአንደበታቸው ካለ ሰይፍ ያድነዋል

እዚህ ስፍራ ሰዎች የሚናገሯቸው ስድቦች እና ማስፈራሪያዎች በአንደበታቸው ለይ የሚገኝ ሰይፍ እንደሆነ ተደርጎ ተገልጽዋል፡፡ "እርሱ ግን ደሃውን ከታላላቆች ማስፈራራት ያድነዋል" ወይም "እርሱ ግን ደሃውን ታላላቆች ሲያስፈራሩት ወይም ሰድቡት ይታደገዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ፍትህ አልባነት አንደበቷን ትዘጋለች

ፍትህ አልባ ሰዎች የተገለጹት መናገርን ማቆም ያለባቸው ተደርገው እና ራሱን ፍትህ አልባነትን ሆነው ነው፡፡ "ይህ ፍትህ አልባነት የራሷን አንደበት እንደምትዘጋ ያህል ነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)