am_tn/job/05/11.md

2.3 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ጸሐፊው በእያንዳንዱ ቁጥር ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤን አንድን ሀሳብ ሁለት የተለያዩ መግለጫዎችን በመጠቀም የሚያስተላልፈው እግዚአብሔር የተጠቁትን ከወደቁበት እንደሚየነሳ እና ተንኮለኞችን እንደሚያወርድ ትኩረት ሰጥቶ ለመግለጽ ነው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ ይህንን የሚያደርገው ዝቅ ባለ ስፍራ ያሉትን ከፍ ለማድረግ ነው

የትሁታን መጎዳት የተገለጸው በዝቅተኛ ስፍራ እንደ ተቀመጡ ተደርጎ ነው፡፡ እግዚአብሔር በሚታደጋቸው ጊዜ፣ ክብርን ይቀበላሉ፡፡ ይህ በሚሆንበት ጊዜ ከፍ ተደርገው በከበረ ስፍራ እንደተቀጡ ተደርጎ ይነገርላቸዋል፡፡ "እግዚአብሔር ይሰቃዩ የነበሩ ትሁታንን ለማዳን እና እነርሱን ለማክበር ይህንን ያደርጋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

እቅዳቸውን ይሰብራል

እዚህ ስፍራ የተንኮለኞችን እቅድ ማስቆም የተገለጸው እነርሱ በአካል እንክት ተደርገው እንደሚሰበሩ ነገሮች ተደርጎ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ተንኮለኛ ሰዎችን በራሳቸው ክፉ ስራ ያጠምዳቸዋል

እዚህ ስፍራ ተንኮለኞችን በራሳቸው ክፉ ስራ እንዲጨነቁ ማድረግ የተገለጸው እነርሱን በወጥመድ እንመያዝ ተደርጎ ነው፡፡ የራሳቸው ድርጊቶች የተነገሩት እነዚያ ወጥመዶች እንደሆኑ ተደርጎ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ጠመዝማዛ ሰዎች

እዚህ ስፍራ በብልጣብልጥነት የሚደረግ ክፋት የተገለጸው ጠመዝማዛ መሆን ተደርጎ ነው፡፡ "ብልጣብልጥ የሆኑ" ወይም "ቅን ያለሆኑ" ወይም "ብልጦች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)