am_tn/job/05/08.md

1.7 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በእነዚህ ቁጥሮች፣ ኤልፋዝ ንግግሩን ከኢዮብ 4፡1 ጀምሮ ይቀጥላል፡፡ ጸሐፊው ኢዮብ አስደናቂ ነገሮች የሚያደርገውን እግዚአብሔርን መለመን እንደሚገባው አጉልቶ ለማሳየት አንድን ሀሳብ ሁለት የተለያዩ አገላለጾች በመጠቀም ለማስተላለፍ በእያንዳንዱ ቁጥር ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ መጠቀሙን ይቀጥላል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ታላቅ እና የማይመረመሩ ነገሮች፣ ቁጥር የሌላቸው አስደናቂ ነገሮች

"ከመረዳት ባሻገር የሆኑ ታላላቅ ነገሮች፣ ሊቆጠሩ የማይችሉ አስደናቂ ነገሮች"

የማይመረመሩ ነገሮች

ይህ የሚያመለክተው የሰው ልጅ ሊረዳቸው የማይችሉ ነገሮችን ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)

ታላቅ እና የማይመረመሩ ነገሮች

እዚህ ስፍራ ጸሐፊው "እና" በሚል የተያያዙ ሁለት ራሳቸውን የቻሉ ቃላትን የሚጠቀመው የእግዚአብሔርን ስራ ታላቅነት ለማጉላት ነው፡፡ "በታላቅነት ጥልቅ/መሰረታዊ የሆኑ ነገሮች" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሄንዲየዲስ/ሁለት ቃላት ‘እና' በሚል አያያዥ ቃል የሚገኛኙበትና አንድን ጥልቅ ሀሳብ ለመግለጽ የሚያገለግል ዘይቤያዊ አነጋገር)

አስደናቂ ነገሮች

"አስገራሚ ነገሮች" ወይም "አስደናቂ ነገሮች"