am_tn/job/05/04.md

2.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ

ይህ ቁጥር ቀደም ሲል ያገለገለ ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ ቅጥያ ነው፣ እዚህ ስፍራ የሞኝ ሰው ልጆች በፍጹም ደህንተታቸው የተጠበቀ እንዳልሆነ በተለያዩ መንገዶች በትኩረት ተገልጽዋል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የእርሱ ልጆች ደህንነትን/ጥበቃ ከማግኘት የራቁ ናቸው

"የእርሱ" የሚለው የሚያመለክተው በኢዮብ 5፡2 ላይ የሚገኘውን ሞኙን ሰው ወይም ሞኝ ሰዎችን ነው፡፡ "ልጆቻቸው ፈጽሞውን ደህንነታቸው የተጠበቀ አይደለም" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ይፈጫሉ

እዚህ ስፍራ መፈጨት የሚለው የሚወክለው በፍትህ አደባባይ በጭቆና ስር መሆንን እና ጥቅምን መቀማትን ነው፡፡ ይህ ሀሳብ በአድራጊ ዐረፍተ ነገር ሊጻፍ ይችላል፡፡ "አንድ ሰው ያደቅቃቸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ እና አድራጊ ወይም ተደራጊ የሚሉትን ይመልከቱ)

የከተማ በር

የከተማ በር፣ ክርክሮች የሚፈቱበት እና ፍትህ የሚሰጥበት ስፍራ ሆኖ ያገለግል ነበር፡፡

የሚታደጋቸው ማንም የለም

"የሞኝ ሰዎችን ልጆች ከመከራቸው ለማውጣት ሊረዳቸው የሚችል ማንም የለም"

ሌላው ቀርቶ ከእሾህ መሃል ይህን ይወስዳሉ

ምናልባት ይህ የሚያመለክተው የእሾህ ተክል ከመኖሩ የተነሳ የከፋው ተክል የሚበቅልበትን ስፍራ ነው

ሃብታቸውን ተጠምቶ የሚፈልግ

እዚህ ስፍራ ስግብግብ ሰዎች የተገለጹት እንደ ተጠሙ ሲሆን፣ የሞኝ ሰው ሃብት ደግሞ እነርሱ ሊጠጡት እንደሚችሉት ነገር ተደርጎ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አገላለጽ የሚለውን ይመልከቱ)