am_tn/job/03/23.md

2.0 KiB

መንገዱ ለተደበቀችበት እግዚአብሔር ላጠረበት ሰው፣ ለምን ብርሃን ተሰጠው?

ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው ዐረፍተ ነገር ለማበጀት ነው፡፡ "እግዚአብሔር ለሰው ህይወት ከሰጠው በኋላ የወደፊቱን ነጥቆ ሊያጥርበት አይገባም" በሚለው ወስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ለሰው ለምን ብርሃን ተሰጠው

እዚህ ስፍራ ብርሃን የሚወክለው ህይወትን ነው፡፡ "እግዚአብሔር ለምን አንድን ሰው በህይወት ያኖረዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

መንገዱ ለተደበቀችበት

እዚህ ስፍራ ኢዮብ አስቀድሞ ስለማያውቀው ስለ ወደፊቱ እግዚአብሔር እንደሰወረበት አድርጎ ይናገራል፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔር መንገዱን ያጠረበት

እዚህ ስፍራ በችግር ውስጥ መሆን እና አደጋዎች የተገለጹት በጠባብ ስፍራ እንደመወሰን ተደርጎ ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ትካዜ ምግብ ሆኖኛል፣ የስቃይ ጩኸቴ/መቃተቴ እንደ ውሃ ይፈሳል

ኢዮብ ጭንቀቱን በሁለት መንገዶች ይገልጻል፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ትካዜ ምግብ ሆኖኛል

"ከመመገብ ይልቅ፣ ሀዘንተኛ ሆኛለሁ"

የስቃይ ጩኸቴ/መቃተቴ እንደ ውሃ ይፈሳል

እንደ ሀዘን የመሰሉ የስነምግባር ባህሪያት እና ስሜቶች ብዙውን ጊዜ በውሃ ይገለጻሉ፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)