am_tn/job/03/11.md

2.1 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

ይህ የንባብ ክፍል ኢዮብ የተለያዩ ተከታታይ ሃሳቦችን ለማቅረብ የሚጠይቃቸውን አራት ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄዎችን ይይዛል

ከማህጸን ሳልወጣ ሞቼ በቀረሁ?

"ለምን በምወለድበት ጊዜ ሳልሞት ቀረሁ?" ኢዮብ ይህንን ጥያቄ የሚያቀርበው የተወለደበትን ቀን ለመርገን እና ጭንቀቱን ለመግለጽ ነው፡፡ "ምነው በተወለድኩበት ቀን በሞትኩ ኖሮ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ምነው እናቴ በወለደችኝ ቀን ነፍሴን ሳልሰጥ ቀረሁ?

ኢዮብ ይህንን የሚለው በህይወት መወለድ አልነበረብኝም ለማለት ነው፡፡ "ምነው ከማህጸን በመጣሁበት ሰአት በሞትኩ ኖሮ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ነፍሴን ብሰጥ

ይህ ሞትን ያመለክታል፡፡ (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ለምን ጉልበቶቿ ታቀፉኝ

ይህ ምናልባት የኢዮብን እናት ጭኖች ሊያመለክት ይችላል፡፡ የእናቱ ጉልበቶች የተገለጹት አዲስ የተወለደን ህጻን እንደሚቀበሉ ሰዎች ተደርጎ ነው፡፡ "እኔን የሚታቀፉ የእናት ጭኖች/ጉልበቶች ባይኖሩ በመደድኩ ነበር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)

እጠባቸው ዘንድ ስለምን የእናቴ ጡቶች ተቀበሉኝ?

የኢዮብ እናት ጡቶች የተገለጹት አዲስ የተወለደን ህጻን እንደሚቀበሉ ሰዎች ተደርጎ ነው፡፡ "የምጠባቸው ጡቶች ባይኖሩ በወደድኩ " በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ እና ሰውኛ ዘይቤ የሚሉትን ይመልከቱ)