am_tn/job/03/04.md

2.6 KiB

አጠቃላይ መረጃ፡

በዚህነዚህ ሀረጋት ውስጥ የሚገኙት አገላለጾች ኢዮብ የተወለደበት ቀን ከእንግዲህ እንዳይኖር ያለን ምኞች የሚገልጹ ናቸው፡፡ ይህ ምናልባት የቀደመው ቀን በአንድ መንገድ የሚቀጥል መሆኑን የሚጠቁም ሊሆን ይችላል፡፡ ዩዲቢ ቀኑ ምን ይመስል እንደነበር የሀዘን መግለጫ አድርጎ ይተረጉማቸዋል፡፡

ያ ቀን ጨለማ ይሁን… ፀሐይም አይውጣበት፡፡

እነዚህ ሁለት ሀረጎች ኢዮብን ጸጸት በመደጋገም የተወለደበትን ቀን ጨለማነቱ ይገልጻሉ፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

ያ ቀን ጨለማ ይሁን

ይህ ያዚያችን ቀን ከእንገዲህ ያለመኖር የሚገልጽ ምኞት ነው፡፡ "ያቺ እለት ትጥፋ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ ( ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ጨለማ እና የሞት ጥላ እርሱን ይውረሱት

እዚህ ስፍራ ጨለማ እና የሞት ጥላ የተገለጹት አንድን ሰው ወይም አንድን ነገር የራሱ እንደሚያደርግ ሰው ተደርገው ነው፡፡ "እርሱን" የሚለው ቃል የሚያመለክተው የኢዮብን የልደት ቀን ነው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)

የሞት ጥላ

እዚህ ስፍራ ጥላ የሚወክለው ሞትን ነው፡፡ "ሞት እንደ ጥላ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ደመና በላዩ ይኑር

እዚህ ስፍራ ደመና የተገለጸው በኢዮብ የልደት ቀን ላይ መኖር እንደሚችል ሰው ተደርጎ ነው፡፡ "ማንም ሊመለከተው እንዳይችል ደመና ይሸፍነው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ቀኑን ጨለማ የሚያደርግ ነገር ሁሉ

ይህ የሚያመለክተው የፀሐይን ብርሃን የሚጋርድን እና መለማ የሚፈጥርን ነገር ሁሉ ነው፡፡ እዚህ ስፍራ "ጥቁር" የሚወክለው ጨለማን ነው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

ያስፈራሩት

"ያንን ቀን ያስፈራሩት፡፡" ቀኑ የተገለጸው በጨለማ ፍርሃት እንደሚውጠው ሰው ተደርጎ ነው፡፡ (ሰውኛ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)