am_tn/job/01/09.md

4.0 KiB

ኢዮብ እግዚአብሔርን የሚፈራው ያለ ምክንያት ነውን?

"ኢዮብ እግዚአብሔርን የሚያከብረው ያለ ምክንያት ነውን?" ሰይጣን ለእግዚአብሔር ጥያቄ አቅርቦ ራሱ መልስ ይሰጣል፡፡ ኢዮብ እግዚአብሔርን የሚታዘዘው እግዚአብሔር ስለባረከው ብቻ ነው ይላል፡፡ "ኢዮብ እግዚአብሔርን ለመታዘዝ ምክንያት አለው" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

በዙሪያው፣ በቤቱ ዙሪያ እና ባለው ነገር ሁሉ ዙሪያ ቅጥር አላኖርክለትምን?

ሰይጣን ክርክሩን ለማጠናከር የሚረዱትን መረጃዎች ሁሉ ይናገራል፡፡ "አንተ እርሱን፣ ቤተሰቡን እና ያለውን ነገር ሁሉ ጠብቀሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

በዙሪያው፣ በቤቱ ዙሪያ እና ባለው ነገር ሁሉ ዙሪያ ቅጥር አድርገህለታል

እንደ ግርግዳ ወይም አጥር ያለ መከላከያ የአንድን ሰው ይዞታ ዙሪያውን እንደሚከብ እና እንደሚጠብቅ፣ እግዚአብሔር ኢዮብን በጥበቃው ከቦታል፡፡ "እርሱን እና ቤቱን እንዲሁም የእርሱ የሆነውን ሁሉ ጠብቀሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ዘይቤያዊ አነጋገር የሚለውን ይመልከቱ)

የእጆቹን ስራዎች

"የሚሰራውን ነገር ሁሉ"

በምድር ላይ ከብቱ በዝቶለታል

"በምድር ላይ ከብቱ ተትረፍርፏል"

ነገር ግን አሁን እጅህን ዘርግተህ ያለውን ሁሉ ንካበት፣ በዚያን ጊዜ ፊት ለፊት እንደማይረግምህ ታያለህ

ሰይጣን ይህንን ማለቱ እግዚአብሔር ኢዮብን ቢነካው፣ የኢዮብ ምላሽ ምን እንደሚሆን ይመለከታል ማለቱ ነው፡፡ "ነገር ግን አሁን፣ እጅህን ብትዘረጋ እና ያለውን ሁሉ ብትነካ ፊት ለፊት እንደሚረግምህ ታያለህ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡

ነገር ግን አሁን፣ እጅህን ዘረጋ

እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚወክለው የእግዚአብሔርን የማድረግ አቅም ነው፡፡ "ነገር ግን አሁን ሀይልህን ተጠቀም" (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

እርሱ ያለውን ሁሉ ንካ

እዚህ ስፍራ "መንካት" የሚወክለው ጉዳት የማድረስ ወይም የማጥፋት ድርጊትን ነው፡፡ "ያለውን ሁሉ አጥፋ" ወይም "ያለውን ሁሉ ደምስስ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በፊትህ

"እየሰማኸው፡፡" ይህ የሚያመለክተው እግዚአብሔር ትኩረት የሚሰጥበትን ጊዜ ነው፡፡

እነሆ

"እነሆ" ወይም "የምናገረውን ትኩረት ሰጥተህ ብትሰማኝ"

እርሱ ያለው ሁሉ በእጅህ ነው

እዚህ ስፍራ "እጅ" የሚወክለው አንድ ሰው አንድን ነገር ለመቆጣጠር ያለውን አቅም/ሀይል ነው፡፡ "እርሱ ባለው ነገር ላይ ሁሉ አቅም ተሰጥቶሃል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)

በእርሱ በራሱ ላይ

"በህይወቱ ላይ"

ያህዌ ከሚገኝበት ወጥቶ ሄደ

"ከያህዌ ፊት ወጥቶ ሄደ" ወይም "ያህዌ ካለበት ለቆ ሄደ"