am_tn/job/01/06.md

2.3 KiB

ከዚያም … የሚደረግበት ቀን ነበር

"በ…በሚሆንበት ጊዜ" ወይም "አንድ ዕለት... በ…ጊዜ፡፡" ይህ በአንድ የተለየ ቀን ብቻ የተደረገ አይደለም፣ ይልቁንም ስብሰባው ብዙውን ጊዜ እንደሚደረግ ግልጽ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ልጆች

ይህ ሰማያዊ ፍጥረታትን፣ መላዕክትን ያመለክታል፡፡

ራሳቸውን በያህዌ ፊት ለማቅረብ

"ያደርጉት ዘንድ እርሱ እንዳዘዛቸው በያህዌ ፊት በአንድነት ለመቆም"

ያህዌ

ይህ እግዚአብሔር በብሉይ ኪዳን ራሱን ለህዝቡ የገለጸበት ስም ነው፡፡ ስለ ያህዌ ይህ እንዴት እንደሚተረጎም የቃል ትርጉም ገጽን ይመልከቱ፡፡

በምድር ከመዞር፣ በላይዋ ከመመላለስ

"መዞር" እና "መመላለስ" የሚሉት ሀረጋት በምድር ሁሉ የመጓዝን ድርጊት በሙላት ለማጉላት የዋለ ነው፡፡ "በምድር ላይ በሁሉም ስፍራ መዞር" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ትይዩ ንጽጽራዊ ዘይቤ እና ጽንፍ የሚሉትን ይመልከቱ)

ባሪያዬን ኢዮብን አይተኸዋልን?

"ስለ ባሪያዬ ኢዮብ አውቀሃልን?" እዚህ ስፍራ እግዚአብሔር ስለ ኢዮብ ከሰይጣን ጋር መነጋገር ይጀምራል፡፡ "ባሪያዬን ኢዮብን አይተኸዋል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ቃለ ምልልሳዊ ጥያቄ የሚለውን ይመልከቱ)

ነቀፋ የሌለበት እና ቅን ሰው

"ነቀፋ የሌለበት" እና "ቅን" የሚሉት ቃላት ተመሳሳይ ትርጉሞችን ሲይዙ ኢዮብ ጻድቅ ሰው መሆኑን አጉልተው ያሳያሉ፡፡ ይህ በኢዮብ 1፡1 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡ "በእግዚአብሔር ፊት መልካም የሆነውን የሚያደርግ" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ጥንድ ትርጉም የሚለውን ይመልከቱ)

እግዚአብሔርን የሚፈራ

"እግዚአብሔርን የሚያከብር፡፡" ይህ በኢዮብ 1፡1 ላይ እንዴት እንደ ተተረጎመ ይመልከቱ፡፡