am_tn/job/01/04.md

2.5 KiB

በእያንዳንዱ ልጅ ተራ፣ እርሱ ያቀርብ ነበር

"ቀን" የሚለው ቃል ምናልባት የአንዱን ልጅ ልደት የሚያከብሩበት ቀን ማለት ሊሆን ይችላል፡፡ ነገር ግን ቢያንስ ልጆቹ በየተራ ድግስ እንደሚያደርጉ ያመለክታል፡፡ "በእያንዳንዱ ልጅ የልደት ቀን፣ ልጁ ያቀርብ ነበር" ወይም "እያንዳንዱ ልጅ በተራው ያቀርብ ነበር"

እርሱ ያቀርብ ነበር… እነርሱ ልከው… ይጠሩ ነበር… ኢዮብ ይልክ ነበር… እርሱ ይሳል ነበር… በጥዋት ማልዶ ተነስቶ መስዋዕት ያቀርብ ነበር... እንዲህ ይል ነበር

"ሁሌም ያቀርብ ነበር…እነርሱ ሁሌም… ልከው ይጠሩ ነበር… ኢዮብ ሁሌም ይልክ… ሁሌም ይሳል… እርሱ ሁሌም ማልዶ ይነሳ እና ይሰዋ… እርሱ ሁሌም እንዲህ ይል ነበር"

ከእነርሱ ጋር

"እነርሱ" የሚለው ቃል የሚያመለክተው ሰባቱን ወንዶች ልጆች እና ሶስቱን ሴት ልጆች ሲሆን ኢዮብን ግን አይጨምርም፡፡

የድግሱ ዕለት ሲያልፍ

"ድግሱ ሲጠናቀቅ" ወይም "ከድግሱ በኋላ"

ኢዮብ ወደ እነርሱ ይልክና

"ኢዮብ ዘወትር እነርሱ ወደ እርሱ እንዲመጡ አንድ ሰው ይልክ ነበር"

እነርሱን ያነጻ ነበር

እዚህ ስፍራ "ማንጻት" ማለት የኢዮብ ልጆች በደስታ በአንድነት ተሰብስበው ግብዣ ሲያደርጉ የፈጸሙት የምልኮ ነቀፊታ ቢኖር ጥፋት እንዳይደርስባቸው እግዚአብሔርን ይቅርታ መለመን ማለት ነው፡፡ ኢዮብ ስለ እነርሱ መስዋዕት በማቅረብ ይህን ያደርግ ነበር፡፡

በልባቸው እግዚአብሔርን ረግመው ቢሆን

"በልባቸው" የሚለው የሚወክለው ሃሳባቸውን ነው፡፡ ብዙውን ጊዜ እንዲህ ያሉ ሃሳቦች አንድ ሰው ነገሩን ሊያስበው ሳይፈልግ ከፈቃዱ ውጭ ሊመጡ ይችላሉ፡፡ "በሃሳባቸው እግዚአብሔርን ረግመው ይሆናል" በሚለው ውስጥ እንደሚገኘው፡፡ (ሜቶኖሚ/ከአንድ ባህሪው በመነሳት ለነገሩ ስያሜ መስጠት የሚለውን ይመልከቱ)