am_tn/jer/07/21.md

1.9 KiB

አያያዥ ሀሳብ፡-

እግዚአብሔር ለይሁዳ ሕዝብ ያለውን መልእክት ለኤርምያስ መስጠቱን ቀጥሏል፡፡

አጠቃላይ መረጃ፡-

በእነዚህ ጥቅሶች ውስጥ “እናንተ” እና “የእናንተ” የሚሉት የይሁዳን ሕዝብ ያመለክታሉ፡፡

የሰራዊት ጌታ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል

ኤርምያስ ብዙ ጊዜ እነዚህን ቃላት የሚጠቀመው ከእግዚአብሔር የመጣውን በጣም ጠቃሚ መልእክት ለማስተዋወቅ ነው፡፡ ይህንን በኤርምያስ 6:6 ላይ እንዴት እንደተረጎምኸው ተመልከት፡፡

የሚቃጠለውን መስዋዕታችሁን በሌሎች መስዋዕታችሁ ላይ ጨምሩ፣ ስጋውንም ራሳችሁ ብሉ

ይህ መስዋዕታቸው በሙሉ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነት እንደሌለው አጽንዖት የሚሰጥ ምጸታዊ ዓረፍተ ሃሳብ ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “ሂዱና የሚቃጠል መስዋዕቶቻችሁን ከመስዋዕታችሁና ከስጋው ጋር አብራችሁ ብሉት” (ምፀት የሚለውን ይመልከቱ)

ድምጼን ስሙ

እዚህ ላይ የእግዚአብሔርን ድምጽ መስማት ቃሉን መስማትና ለተናገረው ደግሞ መታዘዝ ማለት ነው፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “የተናገርሁትን ስሙ ደግሞም ታዘዙ” (ምትክ ስም የሚለውን ይመልከቱ)

ባዘዝኋችሁ መንገድ ሁሉ ሂዱ

እግዚአብሔር ቃሉን ስለመታዘዝ ሲናገር ሰው በመንገድ እንደሚሄድ እንደዚሁ አንድ ሰው በቃሉ መሄድ እንደሆነ አድርጎ ገልጾታል፡፡ አማራጭ ትርጉም፡- “እኔ ያዘዝኋችሁን ሁሉ አድርጉ” (ተለዋጭ ዘይቤ የሚለውን ይመልከቱ)