am_tn/jdg/18/30.md

1.2 KiB

X

ይህ ሚካን በካህንነት ያገለግለው የነበረው የወጣቱ ሌዋዊ ስም ነው። ይህ ግልጽ መደረግ ይችላል። አ.ት፡ “የወጣት ሌዋዊው ስም የሙሴ ልጅ የጌርሳም ልጅ ዮናታን ነበር” ( እና ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ምድሪቱ እስከተያዘችበት ቀን ድረስ

ይህ የዳን ሰዎች በጠላቶቻቸው የሚያዙበትን የወደፊት ጊዜ የሚያመለክት ነው። እዚህ ጋ የምድሪቱ መያዝ በጠላት እንደተማረከ እስረኛ ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ “ጠላቶቻቸው ምድራቸውን እስከያዙበት ቀን ድረስ” ወይም “ጠላቶቻቸው ማርከው እስከወሰዷቸው ቀን ድረስ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)

የሠራቸው

ሚካ አማልክቶቹን አልሠራቸውም፤ ይልቁንም ባለ ሙያ ነበር የሠራለት። አ.ት፡ “ተሠርተዉለት የነበሩት” ወይም “የእርሱ ባለ ሙያ የሠራለት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)