am_tn/jdg/18/24.md

3.2 KiB

የሰራኋቸውን አማልክቶቼን

ሚካ አማልክቶቹን አልሠራቸውም፤ የሠራቸው ባለ ሙያ የሆነ ሰው ነው። አ.ት፡ “ለራሴ ያሠራኋቸውን አማልክት” ወይም “ባለ ሙያ የሠራልኝን አማልክት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ሌላ ምን ቀረኝ?

ሚካ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው ለእርሱ አስፈላጊ የሆኑት ነገርች አሁን እንደሌሉት አጽንዖት ለመስጠት ነው። አ.ት፡ “ምንም የቀረኝ ነገር የለም” ወይም “ለእኔ አስፈላጊ የሆነውን ነገር በሙሉ ወስዳችሁብኛል” (ምላሽ የማይሻ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)

“ምን ሆንክ?” ብላችሁ እንዴት ትጠይቁኛላችሁ

ሚካ ይህንን ጥያቄ የሚጠይቀው የዳን ሰዎች የሆኑት በእርግጥ ምን እንዳሳሰበው እንደሚያውቁ አጽንዖት ለመስጠት ነው። አ.ት፡ “እጅግ እንዳዘንኩ ታውቃላችሁ!” ወይም “በእኔ ላይ ባደረጋችሁት ነገር ምን ያህል እንደተቸገርኩ ታውቃላችሁ!” (ምላሽ የማይሻ ጥያቄ የሚለውን ተመልከት)

ምንም አይነት ነገር ስትናገር እንዳንሰማህ

“ስትናገር እንዳንሰማህ” የሚለው ሐረግ የዳን ሰዎች ሚካ ስለሆነው ነገር የሚያወራውን መስማታቸውን ያመለክታል፤ ነገር ግን ሚካ ስለተፈጠረው ነገር ማውራቱን ከሌሎች ሰዎች መስማታቸውንም ይጨምራል። አ.ት፡ “ምን እንደተናገርክ ማወቅ እንፈልጋለን” ወይም “ስለዚህ ጉዳይ የፈለግኸውን ተናገር” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ምንም አይነት ነገር ስትናገር እንዳንሰማህ

“ምንም ዓይነት ነገር” የሚለው ሐረግ የዳን ሰዎች ወደ ሚካ ቤት መጥተው ጣዖቶቹን መስረቃቸውን የሚጠቁም የትኛውንም መረጃ ያመለክታል። ይህ በግልጽ መነገር ይችላል። አ.ት፡ “ስለዚህ ጉዳይ ምንም ነገር ስትናገር እንዳንሰማህ” ወይም “ስለሆነው ነገር እንዳች ስትናገር እንዳንሰማህ”

አንተና ቤተሰቦችህ ትገደላላችሁ

ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አንተንና ቤተሰብህን እንገላለን” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)

መንገዳቸውን ሄዱ

ይህ ጉዟቸውን ቀጠሉ ማለት ነው። አ.ት፡ “ጉዟቸውን ቀጠሉ” ወይም “መጓዛቸውን ቀጠሉ” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)

ለእርሱ እጅግ የበረቱ ነበሩ

ይህ የሚያመለክተው ሚካና ሰዎቹ እንዳይዋጓቸው የዳን ሰዎች እጅግ ብርቱ መሆናቸውን ነው። አ.ት፡ “እርሱና ከእርሱ ያሉት ሰዎች እንዳይዋጓቸው እጅግ ብርቱዎች ነበሩ”