am_tn/jdg/16/17.md

1.7 KiB

ሁሉንም ነገር ነገራት

ስለ ብርታቱ ምንጭ ሁሉንም ነገር ነገራት። ይህ በግልጽ መነገር ይችላል። አ.ት፡ “የብርታቱን ምንጭ ነገራት” ወይም “እውነቱን ነገራት”

ምላጭ

ከሰው ቆዳ ድረስ ተጠግቶ ፀጉር ለመቁረጥ የሚያገለግል ስለታም መቁረጫ

ለእግዚአብሔር ናዝራዊ

ይህ ማለት እንደ ናዝራዊ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ነበር ማለት ነው። በመሳፍንት 13፡15 ያለውን ተመሳሳይ ሐረግ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “ለእግዚአብሔር የተሰጠ ናዝራዊ” ወይም “እንደ ናዝራዊ ለእግዚአብሔር የተሰጠ”

ከእናቴ ማህፀን

እዚህ ጋ “ከእናቴ ማህፀን” የሚያመለክተው የተወለደበትን ጊዜ ነው። ይህ ማለት ከተወለደበት ጊዜ ጀምሮ ናዝራዊ ነበር ማለት ነው። አ.ት፡ “ሕይወቴን በሙሉ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ፀጉሬ ከተላጨ

ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “አንድ ሰው ፀጉሬን ቢላጨኝ” (አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)

ተላጨ

ወደ ቆዳ አስጠግቶ ፀጉርን በምላጭ መቁረጥ

ኃይሌ ከእኔ ይሄዳል

ሳምሶን ስለ ብርታቱ ትቶት ሊሄድ እንደሚችል ሰው አድርጎ ይናገራል። አ.ት፡ “ከእንግዲህ ወዲህ ብርቱ አልሆንም” (ሰውኛ የሚለውን ተመልከት)