am_tn/jdg/13/03.md

1.9 KiB

ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ

ይህ የሕፃን ልጅን መወለድ ያመለክታል። አ.ት፡ “ወንድ ልጅ መውለድ” ወይም “ወንድ ሕፃን ልጅ ይኖርሻል” (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)

ንጹሕ ያልሆነ ምንም ነገር

እግዚአብሔር መበላት የለበትም ያለው ነገር በአካላዊነቱም ንጹሕ እንዳይደለ ተነግሯል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

እነሆ

“አስተውይ” ወይም “አድምጪ”

በራሱ ላይ ምላጭ አያርፍበትም

እዚህ ጋ “ራስ” የሚያመለክተው ጸጉሩን ነው። ይህ በአድራጊ ድምፅ ሊነገር ይችላል። አ.ት፡ “ማንም ጸጉሩን እንዳይቆርጠው”(አድራጊ ወይም ተደራጊ ድምፅ የሚለውን ተመልከት)

ምላጭ

ጸጉርን ከቆዳ አጠገብ አድርሶ ለመቁረጥ የሚያገለግል ስል ቢለዋ ነው

ለእግዚአብሔር ናዝራዊ

ይህ ማለት እንደ ናዝራዊ ለእግዚአብሔር የተሰጠ ይሆናል ማለት ነው። አ.ት፡ “ለእግዚአብሔር የተሰጠ ናዝራዊ” ወይም “እንደ ናዝራዊ ለእግዚአብሔር የተሰጠ”

ከማህፀን

እዚህ ጋ “ማህፀን” የሚያመለክተው ሕፃን ከመወለዱ በፊት ያለውን ጊዜ ነው። አ.ት፡ “ከመወለዱ በፊት” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ከፍልስጥኤማውያን እጅ

እዚህ ጋ “እጅ” መቆጣጠር ማለት ነው። አ.ት፡ “ከፍልስጥኤማውያን ቁጥጥር” ወይም “በፍልስጥኤማውያን ቁጥጥር ስር ከመሆን” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)