am_tn/jdg/13/01.md

1.3 KiB

በእግዚአብሔር ፊት ክፉ የሆነውን

የእግዚአብሔር ፊት የእርሱን ፍርድ ወይም ምዘና ይወክላል። ይህንን በመሳፍንት 2፡11 ላይ እንዴት እንደተረጎምከው ተመልከት። አ.ት፡ “በእግዚአብሔር ፍርድ ክፉ የሆነውን” ወይም “እግዚአብሔር ክፉ ነው ያለውን” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

በፍልስጥኤማውያን እጅ ሰጣቸው

እዚህ ጋ “እጅ” የሚወክለው በጦርነት ድል ማድረጊያ ኃይልን ነው። አ.ት፡ “ፍልስጥኤማውያን እንዲያሸንፏቸው ፈቀደ” ወይም “በፍልስጥኤማውያን እንዲጨቆኑ ፈቀደ” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

አርባ ዓመት

“40 ዓመት” (ቁጥሮች የሚለውን ተመልከት)

ጾርዓ

ይህ በእስራኤል የነበረ ከተማ ስም ነው። እርሱ በዳን ድንበር አቅራቢያ በይሁዳ አውራጃ ነበር። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ዳናውያን

የዳን ነገድ ሰዎች

ማኑሄ

ይህ የሰው ስም ነው። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)