am_tn/jdg/11/34.md

1.8 KiB

አታሞ

እንደ ከበሮ የሚመታበት አናት ያለው፣ በሚንቀሳቀስበት ጊዜ ድምፅ እንዲያሰማ በዙሪያው ቁርጥራጭ ብረቶች የሚደረጉለት የሙዚቃ መሣሪያ።

ልብሶቹን ቀደደ

ይህ ለቅሶን ወይም ታላቅ ሐዘንን የሚያሳይ ድርጊት ነው። አ.ት፡ “ልብሱን በሐዘን ቀደደ” (ምሳሌአዊ ድርጊት የሚለውን ተመልከት)

በሐዘን ሰበርሽኝ -- ለህመም ዳረግሽኝ

ዮፍታሔ አንዱን አሳብ ሁለት ጊዜ መናገሩ እጅግ ስለ ማዘኑ አጽንዖት ለመስጠት ነው።

በሐዘን ሰበርሽኝ

እዚህ ጋ፣ ዮፍታሔ ጥልቅ ሐዘኑን እንደሚሰባብረው አንደ አንዳች ነገር ቆጥሮ ይናገራል። አ.ት፡ “ጥልቅ ሐዘን ላይ ጥለሽኛል” ወይም “በሐዘን እንድሞላ አደረግሽኝ”። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ለህመም ዳረግሽኝ

እዚህ ጋ ዮፍታሔ የሚናገረው ጥልቅ ሐዘኑና ሥቃዩ እንደ ሕመም እንደሆነበት ነው። አ.ት፡ “አንቺ ሥቃይ እንደሚያመጣብኝ ዓይነት ሰው ሆነሻል” ወይም “ለጥልቅ ሐዘን ዳርገሽኛል”። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ቃሌን ማጠፍ አልችልም

ይህ የአነጋገር ዘይቤ ነው። ቃልን ማጠፍ ማለት ልታደርገው ቃል የገባህበትን ጉዳይ መተው ነው። አ.ት፡ “ቃል የገባሁበትን ጉዳይ መፈጸም አለብኝ” ወይም “ቃሌን ለማጠፍ አልችልም”። (የአነጋገር ዘይቤ የሚለውን ተመልከት)