am_tn/jdg/05/14.md

1.4 KiB

ሥሩ በአማሌቅ ከሆነው ከኤፍሬም

የኤፍሬም ሰዎች የሚኖሩበት ምድር በመጀመሪያ የአማሌቅ ተወላጆች ይኖሩበት ስለ ነበረ የኤፍሬም ሰዎች በምድሪቱ እንደ ተተከሉና ስር እንደ ሰደዱ ተደርጎ ተነግሯል። አ.ት፡ “በአንድ ወቅት የአማሌቅ ተወላጆች ይኖሩ ከነበሩበት ከኤፍሬም ምድር” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ተከተሉህ

እዚህ ጋ “ተከተሉህ” የሚያመለክተው የኤፍሬምን ሕዝብ ነው። በሦስተኛ መደብ ሊነገር ይቻላል። አ.ት፡ “ተከተሏቸው” (የአንተ ቅርጾች እና አንደኛ፣ ሁለተኛ፣ ወይም ሦስተኛ መደብ የሚለውን ተመልከት)

ማኪር

ይህ የማኪር ተወላጆች ይኖሩ የነበሩበት ስፍራ ነው። ማኪር የምናሴ ልጅና የዮሴፍ የልጅ ልጅ ነበር። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ከዛብሎን፣ እነዚያ የአለቅነትን በትር የያዙ

ወታደራዊ አመራሮች የስልጣናቸው ምልክት በሆነው በትራቸው ይገለጻሉ። አ.ት፡ “የዛብሎን ወታደራዊ መሪዎች” (ፈሊጣዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)