am_tn/jdg/02/11.md

1.9 KiB

በእግዚአብሔር ፊት ክፉ የሆነውን

የእግዚአብሔር ፊት የሚወክለው ፍርዱን ወይም ምዘናውን ነው። አ.ት፡ “በእግዚአብሔር ፍርድ ክፉ የሆነውን” ወይም “እግዚአብሔር ክፉ ነው ያለውን” (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

የበኣል አማልክትን

ይህ የበኣል ብዙ ቁጥር ነው። “በኣል” የአንድ ሐሰተኛ አምላክ ስም ሆኖ ሳለ ቃሉ አብዛኛውን ጊዜ ከበኣል ጋር ለሚመለኩ ለሌሎች የተለያየዩ አማልክትም ጥቅም ላይ ውሏል። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)

ከእግዚአብሔር ተለዩ

ከእንግዲህ እግዚአብሔርን የማይታዘዙ እስራኤላውያን፣ በአካል ከእርሱ እንደተነጠሉና እንደተዉት ተቆጥሮ ተነግሯል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

አባቶቻቸው

“አያቶቻቸው” ወይም “የቀደሙት አባቶቻቸው”

ሌሎች አማልክትን ተከተሉ

የእስራኤላውያኑ ሐሰተኞች አማልክትን ማምለክ መጀመር እስራኤላውያን ሐሰተኞች አማልክትን ተከትለው እንደሄዱ ተቆጥሮ ተነግሯል። (ዘይቤአዊ አነጋገር የሚለውን ተመልከት)

ሰገዱላቸው

ይህ የአምልኮትና ለአንድ ሰው አክብሮትን የመስጠት ተግባር ነው።

እግዚአብሔርን ለቁጣ አነሣሡት

“እግዚአብሔር እንዲቆጣ አስደረጉት”

አስታሮቶች

ይህ የአስታሮት ብዙ ቁጥር ሲሆን በተለያዩ ቅርጾች የምትመለክ እንስት አምላክ ናት። (ስሞች እንዴት እንደሚተረጎሙ የሚለውን ተመልከት)