am_tn/isa/34/16.md

1.9 KiB

በእግዚአብሔር መጽሐፍ ፈልጉ

የእግዚአብሔር መጽሐፍ ማለት እግዚአብሔር የተናገረውን መልእክት የያዘ ማለት ነው፡፡ አት፡- "የእግዚአብሔርን መልእክት በያዘው መጽሐፍ ውስጥ የተጻፈውን በጥንቃቄ አንብብ' (ባለቤትነት ተመልከት)

ከእነዚህ አንዱ

"ከእንስሳቱ አንዱ'

ጓደኛውን የሚያጣ የለም

ይህ በአዎንታዊ አረፍተ ነገር ሊገለጽ ይችላል፡፡ አት፡- "እያንዳንዱ እንስሳ ጓደኛ ይኖረዋል' (ድርብ አሉታዊ ተመልከት)

አፉ አዝዞአልና

ለተናገረው አጽንዖት ለመስጠት እግዚአብሔር በአፉ ተወክሏል፡፡ አት፡- "እግዚአብሔር አዝዞልና' (ተለዋጭ ስም ተመልከት)

ለስፍራቸውም ዕጣ ጣለላቸው

ይህ እግዚአብሔር እንስሳት የት መኖር እንዳለባቸው መወሰኑ ለስፍራቸው በተጨባጭ ዕጣ እንደጣለላቸው ተደርጎ ተነግሮአል፡፡ አት፡- "የት እንደሚኖሩ ወሰነ' (ስዕላዊ ንግግር ተመልከት)

እጁም በገመድ ለካችላቸው

ይህ በመጽሐፍ ቅዱስ ዘመን ሰዎች ነገሮችን የሚለኩበትን መንገድ ያመለክታል፡፡ አት፡- "ለእንስሳት መኖሪያቸውን ሰጣቸው'

ከትውልድ እስከ ትውልድ ድረስ

ከትውልድ እስከ ትውልድ የሚለው ሐረግ ወደፊት የሚኖሩትን የሰዎች ትውልዶች ሁሉ ያመለክታል፡፡ ከትውልድ እስከ ትውልድ የሚለውን ሐረግ በኢሳይያስ 13፡20 እንዴት እንደተረጎምህ ተመልከት፡፡ አት፡- "ለዘላለም' ወይም "ሁልጊዜ' (ፈሊጣዊ ንግግር ተመልከት)