am_tn/isa/29/05.md

1.3 KiB

የወራሪዎችሽ ብዛት እንደ ደቀቀ ትቢያ፣ የጨካኞችም ብዛት እንደሚያልፍ ገለባ ይሆናል

ወራሪው ሠራዊት በእግዚአብሔር ምን ያህል ደካማና እዚህ ግባ የማይባል መሆኑን አጽንዖት ይሰጣል፡፡ አት፡- "እግዚአብሔር የወራሪዎችሽን ብዛትና የጨካኞቹን ብዛት በቀላሉ ያስወግዳል፡፡' (ዘይቤአዊ ንግግር ተመልከት)

የወራሪዎችሽ ብዛት

ጥቃት የሚያደርሱብህ ብዙ ወታደሮች

ጨካኞቹ … እንደ ገለባ

ተርጓሚው "ይሆናሉ' የሚለውን ማሰሪያ አንቀጽ መጠቀም ይችላል፡፡ አት፡- "ምሕረት የማያሳዩሽ ወታደሮች እንደ ገለባ ይሆናሉ' (መቅረታቸው አሳቡን ከመረዳት ስለማያጓድሉ የተዘለሉ ተመልከት)

የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ወደ አንቺ ይመጣል

አንቺ የሚለው ቃል የኢየሩሳሌምን ሕዝብ ያመልክታል፡፡ ሊሆኑ የሚችሉ ትርጉሞች፡- 1) "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሊረዳሽ ይመጣል' ወይም 2) "የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ሊቀጣሽ ይመጣል' (የ "አንተ' ልዩ ልዩ አጠቃቀሞች)