am_tn/isa/09/20.md

1.2 KiB

በቀኝ እጃቸው ይነጥቃሉ፤… በግራ እጃቸው

ይህ ማለት ምግብ ካገኙ ይነጥቃሉ ማለት ነው፡፡

እያንዳንዱ የገዛ ክንዱን እንኳ ይበላል

ይህም ማለት 1) ሰዎች የገዛ ክንዳቸውን እንኳ እስኪበሉ ድረስ በጣም ይራባሉ ማለት ሊሆን ይችላል ወይም 2) ‹‹ክንድ›› የሰውየው ወገን ማለት ሊሆን ይችላል፡፡

በዚህ ሁሉ ቁጣው ገና አልበረደም፤ ይልቁን እጁ

‹‹ይህ ሁሉ ሆኖ እንኳ አሁንም እንደ ተቆጣ ነው፤ እጁም›› ኢሳይያስ 5፥25 ላይ ይህን እንዴት እንደ ተረጐምኸው ተመልከት፡፡

አሁንም እጁ እንደ ተዘረጋ ነው

ኢሳይያስ ያህዌን ሌላውን ሰው ለመምታት እጁን ከዘረጋ ሰው ጋር ያመሳስለዋል፡፡ ይህ ያህዌ እስራኤልን የመቅጣቱ ምሳሌ ነው፡፡ ኢሳይያስ 5፥25 ላይ ይህን እንዴት እንደ ተረጐምኸው ተመልከት፡፡ አማራጭ ትርጒም፣ ‹‹አሁንም እነርሱን ለመቅጣት እንደ ተዘጋጀ ነው››