am_tn/gen/49/24.md

1.8 KiB

አጠቃላይ መረጃ

ያዕቆብ ዮሴፍንና ዘሩን መባረክ ይቀጥላል

ቀስቱ ጸና

ቀስቱን የያዘው ሰው መጽናቱ ቀስቱ ራሱ እንደጸና ተደርጐ ተግልጾአል ወደ ጠላቱ በሚያልምበት ጊዜ ቀስቱ እንደሚጸና ይገልጻል አት ወደ ጠላቱ በሚያልምበት ጊዜ ቀስቱን አጽንቶ ይይዛል (ምትክ ቃላት አጠቃቀም እና ግምታዊ እውቀትና ጥልቅ መረጃ ይመልከቱ)

ቀስቱ….እጆቹ

እዚህ “እርሱ” ዘሩን የሚወክለውን ዮሴፍን ነው አት “ቀስቶቻቸውና እጆቻቸው” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)

እጆቹ ቀልጣፋ ይሆናሉ

ቀስትን መያዘ የለመዱ እጆች ስለሆኑ ሙሉ ሰው እንደ እጆች ተገልጾአል:: (ክፍልን እንደሙሉና ሙሉን እንደክፍል የመግልጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ኃያል አምላክ እጆች

እጆች የእግዚአብሔርን ኃይል ይገልጻሉ:: አት “የሁሉን ቻይ አምላክ ኃይል” (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)

ከእረኛው ስም የተነሣ

እዚህ ስም ሙሉ ሰው ይወክላል አት ከእረኛው የተነሣ (ምትክ ቃላት ይመልከቱ)

እረኛው

ያዕቆብ እግዚአብሔር እረኛ እንደሆነ ይናገራል አት ይህም እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚመራና እንደሚጠብቅ ይናገራል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ዐለት

ያዕቆብ እግዚአብሔር ሰዎች የሚወጡበትና ከጠላቶቻቸው የምድኑበት አለት እንደሆነ ይናገራል ይህ የሚያጐላው እግዚአብሔር ሕዝቡን እንደሚጠብቅ ነው (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)