am_tn/gen/49/07.md

1.6 KiB

ቁጣቸው ርጉም ይሁን ጽኑ ነበርና ንዴታቸው ጭከና የተሞላ ነበርና

እግዚአብሔር ስምዖንና ሌዊን የሚረግመው እግዚአብሔር ቁጣቸውንና ንዴታቸውን እንደሚረግም ተደርጐ የገልጾአል:: (ዘይቤያዊ አነጋገርና ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ)

ቁጣቸው የተረገመ ይሁን

አብዛኛውን ጊዜ ነብይ ትንቢትን ሲናገር የሚናገረው ቃል እግዚአብሔር እንደሚናገር ይቆጠራል:: ይህም የሚናገረው ነበዩና እግዚአብሔር እንዴት እንደተቆራኙ ነው::

ንዴታቸው ጭከና የተሞላ ስለነበር

እረግማለሁ የሚለው ቃል የታወቀ ነው አት ንዴታቸው ጭከናን የተሞላ ስለሆነ እረግማለሁ (የተደበቁትን የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

እኔም በያዕቆብ እከፋፍላቸዋለሁ በእስራእልም እበትናቸዋለሁ

“እኔ” እግዚአብሔርን ያመለክታል:: “እነርሱ” ስምዖንንና ለዊን ቢሆንም ምትክ ቃል ስለሆነ ለትውልዳቸውም ይሆናል:: “ያዕቆብ”ና “እስራኤል” ተወራራሽ ስሞችና የእስራእል ሕዝብ የሚተኩ ናቸው:: አት ትውልዳቸውን እበትናለሁ በእስራኤልም ሰዎች መካከል አሠራጫለሁ (ምትክ ቃላትና ተመሣሣይ ተነጻጻሪ አባባል ይመልከቱ)