am_tn/gen/49/05.md

1.5 KiB

ስምዖንና ሌዊ ወንድማማቾች ናቸው

ይህ በትውልድ ወንድሞች መሆናቸውን አይገልጽም ያዕቆብ የሴኬም ሰዎችን ለመግደል አብረው መሥራታቸውን ለማተኮር ነው፡፡

ሰይፎቻቸው የዐመጽ መሣሪያ ናቸው

ሰዎችን ለመጉዳትና ለመግደል ሰይፎቻቸውን ይጠቀማሉ

ነፍሴ …. ልቤ

ያዕቆብ ራሱን ለመግለጽ ነፍሴ እና ልቤ የሚሉ ቃሎችን ይጠቀማልና ክፋን ለማድረግ ከሚያቅዱት ጋር ባለመተባበሩ ሌሎች ሰዎችና እግዚአብሔርም ደግሞ እጅግ እንዳከበሩት ይናገራል (ክፍልን እንደ ሙሉና ሙሉን እንደ ክፍል የመግለጽ ዘይቤ ይመልከቱ)

ወደ ሸንጐአቸው አልግባ

ጉባዔያቸው ውስጥ አልገኝ እነዚህ ሁለቱ ሀረጐች በመሠረቱ ተመሣሣይ ትርጉም አላቸው ያዕቆብ ሁለቱን በማገናኘት በክፉ እቅዳቸው እንደማይሳተፍ አበክሮ ይገልጻል አት ማንኛውንም እቅድ ለማዘጋጀት ከእነርሱ ጋር አልተባበርም (ተመሣሣይ ተነጻጻሪ ይመልከቱ)

የቤሬዎችን ቋንጃ ቈራርጠዋል

ስምዖንና ለዊ ለዕይታ ብለው ቤሬዎችን አስነክሰዋል

ቋንጃ መቈረጥ ወይም ማስነከስ

ይህ የእንስሳትን ቋንጃ በመቁረጥ እንዳይራመዱ ማድረግ ነው