am_tn/gen/44/27.md

2.6 KiB

ይሁዳ ታሪኩን ለዮሴፍ መናገርን ቀጠለ

እንዲህ አለን ሚስቴ ሁለት ወንዶች ልጆችን እንደወለደችልን እናንተ ታውቃላችሁ አንዱ ከእኔ ወጣ አውሬ በላው አላችሁኝ እስከ ዛሬም አላየሁትም ይህንም ከእኔ ለይታችሁ ደግሞ ብትወስዱ ክፉም ቢያገኘው ሽበቴን በሐዘን ወደ መቃበር ታወርዱታላችሁ ይህ ሁለት ደረጃና ሶስት ደረጃ ጥቅሶችን ይዞአል እነዚህም እንደተዘዋዋሪ ጥቅሶች ሊገለጹ ይችላሉ አት እንዲህ አለን ሚስቱ ራሔል ሁለት ወንዶች ልጆችን ብቻ እንደወለደችለት እናውቃለን ከእነርሱ አንዱ ወጣና አውሬ በላው እናም እስከ ዛሬ አላየሁትም ሌላውን ልጅ ብንወስደውና ክፉ ቢያገኘው በሐዘን እንዲሞት እናደርጋለን (ጥቅስን በጥቅስ ውሰጥ እና ቀጥታና ተዘዋዋሪ ጥቅሶችን ይመልከቱ)ከዚይ አለ

እኛን እንዲህ አለን

እዚህ “እኛ” ዮሴፍን አያካትትም (ነጠላና ብዙ ወይም አካታች “እኛ” ይመልከቱ)

እናንተ ታውቃላችሁ

እዚህ “እናንተ” ብዙና ወንድሞቹን ያመለክታል (“እናንተ” አጠቃቀም ዓይነት ይመልከቱ)

በእውሬ ተበላ

ይህ ተሻጋሪ ግሥ በያዘ መልክ ሊገለጽ ይችላል አት አውሬ በላው ተሻጋሪ ግሥ ወይም የማይሻገር ግሥ የያዘ ዐረፍተ ነገር ይመልከቱ

ጉዳት ቢደርስበት

ለአንድ ሰው አንድ ክፉ ነገር የሚደርሰበት ጉዳት ወደዚያ ሰው እንደሚመጣ ተደርጐ ተቆጥሮአል (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሽበተን በሐዘን ወደ መቃብር ታወርዱታላችሁ

“ወደ መቃብር ማውረድ” እንዲሞትና ወደ መቃብር እንዲወርድ ማድረግ ማለት ነው:: “ማውረድ” የሚለውን ቃል የተጠቀመው መቃብር በመሬት ውስጥ እንደሆነ በተለምዶ የታወቀ ስለሆነ ነው:: አት “ከዚያም እኔን ሽማግሌውን በሐዘን እንዲሞት ታደርጋላችሁ” (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

ሽበቴን

ያዕቆብን የሚያመለክትና ሽምግልናውን አበክሮ የሚናገር ነው:: አት “እኔ ሽማግለው” (ምትክ ቃል አጠቃቀም ይመልከቱ)