am_tn/gen/41/50.md

1.9 KiB

የራብ ዓመታት ከመምጣታቸው በፊት

ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመምጣቱ በፊት ይህም አንድ ነገር ተጉዞ ወደ አንድ ቦታ እንደሚመጣ ተደርጐ ስለሚመጡ ዓመታት ይናገራል:: አት “ሰባቱ የራብ ዓመታት ከመጀመራቸው በፊት” (ዘይቤያዊ አነጋገር ይመልከቱ)

አስናት

የአንዲት ሴት ስም ነው:: በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

የዖን ካህን

ዖን የጸሐይ አምላክ ራአ አምልዕኮ ማዕከል ያለባትና “የጸሐይ ከተማ” የሆነች እንዲሁም “ሄልዮቱ” ተብላ የሚትጠራ ከተማ ነች፡፡ በዘፍጥረት 41:45 ይህን እንዴት እንደተረጐሙ ይመልከቱ (ስሞችን ስለመተርጐም ይመልከቱ)

ምናሴ

ተርጓሚዎች የሚከተለውን በግርጌ ማስታወሻ ሊጠቀሙ ይችላሉ:: “ሚናሴ” የሚለው ስም ለመርሳት ምክንያት መሆን ማለት ነው::

የአባቴንም ቤት

ይህ የዮሴፍ አባት ያዕቆብንና ቤተሰቡን ያመለክታል

ኤፍሬም

ተርጓሚዎች የሚከተለውን የግርጌ ማስታወሻ ሊጨምሩ ይችላሉ:: “ኤፍሬም” የሚለው ስም “ፍሬያማ መሆን” ወይም “ልጆችን መውለድ” ማለት ነው::

ፍሬያማ አደረገኝ

“ፍሬያማ” መበልጸግ ወይም ልጆችን መውለድ ማለት ነው:: (ፈሊጣዊ አነጋገር ይመልከቱ)

በተሠቃየሁበት ምድር

“ሥቃይ” የሚለው ረቂቅ ስም “መከራ ተከበልኩ” በሚለው ሊገለጽ ይችላል:: አት “መከራን በተቀበልሁት ምድር” (ረቂቅ ስሞች ይመልከቱ)